fbpx

ወዲ ታጋይ አቶ ጌታቸው ረዳ ጋር የተደረገው ቃለ መጠይቅ በአጭሩ

ወዲ ታጋይ አቶ ጌታቸው ረዳ ጋር የተደረገው ቃለ መጠይቅ ባአጭሩ


* የትግራይ ሰራዊት ብቃት መግለፅ ኣይጠበቅብኝም፣ ለህልውናው የሚታገል ብቃት ያለው ሰራዊት ነው። 

* እቶቼ ወንድሞቼ፣ ኣባቶቼ እናቶቼ ክብሬ ኣሳልፌ ኣልሰጥም ያለ ሰራዊት ነው።


* በትግራይ ላይ የተቀሰሩ ጣቶች እንዲቆጠቡ የተሰማራ ሰራዊት ነው። ስለ ሰራዊቱ ሚልየን ብንናገር የሚበቃ ኣይመስለኝም። 


* በጦርነት ሊዘጉት ያልቻሉትን ጉሮሮ በመብራት፣ በስልክ በመንገድ መዝጋት ሊተገብሩት እየጣሩ ነው። 


* ኣማራ ክልል የገባነው እነ ኣገኘሁ እና ኣብይ እንደሚያወሩት ሳይሆን፣ በትግራይ እናቶች የተቀሰሩ ጣቶች ለማስታገስ ነው።


* በገባንባቸው የኣማራ ክልል ከተሞች ህዝቡ ራሱን በራሱ እንዲያስተዳድር እያደረግን ነው። 


* በገባንባቸው ከተሞች ህዝቡ በደስታ እየተቀበለን ነው፣ በደስታ የሚቀበለን እንደግል ኣዳኝ ቆጥሮን ኣይደለም እህቶቹ እናቶቹ ላይ ሲተኩስ ስላላየው ነው። 


* እነ ኣብይ እና ኣገኘሁ ኣንዳንዴ እንደ ኣሸማጋይ፣ ኣንዳንዴ ነብያት ሁነው ለመኖር ነው የሚፈልጉት ግን ኣንፈቅድላቸውም።


* ላሊበላ ስንገባ ላሊበላን እንዳትነኩ ብለው የጠየቁ ኣሉ፣ ስለ ኣክሱም እና ስለ ኣልነጃሺ የተናገረ ግን ማንም ኣልነበረም። 


* የትግራይ ሰራዊት ስም ለማጉደፍ እና ታሪካቸውንም ጭምር ምንም ስለ ማይመስላቸው ራሳቸውም ሊመቱት ይችላሉ። 


* ህዝቡ የምትፈልጉዋቸው ወንበዴዎች ካሉ ንገሩን ራሳችን መንጥረን እንሰጣቹሃለን እያለን ነው። 


* በገባንበት ሁሉ ጠብመንጃው ጭራሮ ኣስመስሎ እየተወያየ ነው። 


* ራያና ወልቃይት ከተያዘ ራሴን ኣጠፋለሁ ያለው ኣገኘሁ ተሻገር ኣሁን ወደ ስልጣኔን እለቃለሁ የሚል ቀይሮታል። 


* ወልድያ ውግያ እየተካሄደ ቆቦ ይልሻል፣ ጨጨሆ ውግያ እየተደረገ ወልድያ ይልሻል። በዚህ ነው ልሸውዱት የሚፈልጉት። 


* እነዚህ ቅርሻቶች ለዚህ ህዝብ እያስተዳድሩ ስታይ ፣ እነዚህ እንዲፈጠሩ ኣስተዋፅኦ ማድረግህ ይቆጭሃል። 


* ብልፅግና በራያ ግንባር እያለ ይፎክራል፣ ራያ ግንባር ወፍ የለም። 


* ለምንድነው የሚዋሹት? ውሸት የስራቸው ኣልፋና ኦሜጋ ስለሆነ ነው። 


* የኣማራ ወጣት የማይክል ጃክሰን they don’t really care about us የሚለውን ዘፈን ሰምተው ለነ ደመቀ ይህንን ነው ማለት ያለባቸው። 


* ኣወል ኣርባ የኣብይ የሳሎን ውሻ ነው፣ የኣብይ ፈገግታ ካየ በቃ በዛው ይረካል። 


* ዓፋር ክልል ላይ ያለው ጋሊኮማ ኣይደል 10 ሺ ተፈናቃይ፣ እዛ ኣከባቢ 10 የሚያህል ኗሪ የለም። 


* ዓፋር ውስጥ ያሉ ወጣቶች ኣታግሉን ነው እያሉን ያሉት። 


* ህፃን ኣይገደልብኝ ብሎ የተነሳ ሰራዊት ህፃን በመግደል ትግሉን ኣያሳካም። 


* ኣብይ መንግስቱ ሃይለማርያም ለመምሰል የነበረው ፍላጎት በተሟላ መልኩ እየተገለፀበት ያለ ሁኔታ ነው ያለው። መልካቸው ሳይመሳሰል ኣይቀርም ኣሁን። 


* ምዕራብ ትግራይ ነፃ እናወጣዋለን። እነሱ ስለ ማይችሉት ለሻዕቢያ ሊሰጡት እየተደራደሩ ናቸው። ሻዕቢያ ይግባ እናሳየዋለን። 


* የኣማራ ልዩ ሃይል እየተዋጋ መከላከያ ወደ ኃላ እየሸሸ ብለው ነው የሚያወሩት ፣ ሁሉም እየተዋጉ እየቀጣናቸው ነው ያሸነፍነው። 


* የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የቀረው ታንኩ፣የቀረው ሮኬቱ፣የቀረው መድፉ፣ የቀረው ኣሻንጉሊቱ ይዞ ተዋግቷል። ተሟርካል።


* ኣዳዲስ የጦር መሳርያ እየገዛ እንደሆነ መረጃው ኣለን፣ ድሮንም፣ታንክም፣ ዲሽቃም መድፍም እየገዛ ነው፣ እናውቃለን። 


* ክተት የተባለው የዘር ማጥፋት ድርጊቱ ህዝባዊ ተሳትፎ እንዲኖረው ተፈልጎ የተሰራ ነው። 


* የትግላችን ኣልፋና ኦሜጋ የትግራይ ህዝብ መብት ማስከበር ነው። 


* የሰሜን እና የደቡብ ዕዝ ኣዛዦች ክንዱ በዙ፣ ሰለሞን ኢተፋ ላሊበላ ላይ፣ ወልድያ ላይ ምን ሲሰሩ ነበር ብለው ይጠይቋቸው፣ ካገኙዋቸው። 


* ተኩስ ኣቁም ላይ ነበርኩ የሚለው ኣብይ፣ ሰራዊቱ ደብረ ዘቢጥ፣ ጨው በር፣ ዓዲ ኣርቃይ፣ ወልድያ ከነ ታንኩ ምን ሲሰራ ነበር? 


* እኔ ከሞትኩ ሰርዶ ኣይብቀል የሚለው ለኣህያ ተሰጣት እንጂ፣ ይህንን ድርጊት ለኣብይ ነው የሚገልፀው። 


* መወልወያ እና ‘መሽረፈት’ የሚሸጡ የትግራይ ተወላጆች ተግፈተዋል። 


* እየሸሸህ መማረክ ኣትችልመ፣ እየተገረፍክ እንዴት ነው የምትማርከው? ሳትዋጋ እንዴት ነው የምትማርከው። 


* ብዙዎች እየተጠነቀቃችሁ ከኣብይ መቃብር ብትርቁ መልካም ነው። 


ቴሌቪዥን ትግራይ 05 ሓምሌ 05/2013 ኣቆፃፅራ ግዕዝ

Via Kibrom Mulugeta

1120cookie-checkወዲ ታጋይ አቶ ጌታቸው ረዳ ጋር የተደረገው ቃለ መጠይቅ በአጭሩ
%d bloggers like this: