ሰበር ዜና
የትግራይ ሰራዊት ደሴ መቆጣጠር ጀምሯል::
ጀግናው የትግራይ ሰራዊት ኣስቀድሞ ባወጣው እቅድ መሰረት በጣም ብዙ የፋሽስት አብይ አሕመድ ክፍለ ጦሮች በሚያስደንቅ ፅናትና ጀግንነት በመደምስስ ደሴ ከተማ መቆጣጠር ጀምሯል።
አሁንም ቢሆን ውጊያው ከከተማ ውጭ ለመጨረስ ሰራዊታችን የተቻለው ሁሉ በማድረግ ላይ ይገኛል።
ይሁን እንጂ የተሸነፈው ጠላት መሃል ከተማ መድፍ ጠምዶ በመተኮስ ላይ የሚገኝ ሆኖ ሰራዊታችን ሰላማዊ ህዝብ ላለ መጉዳት ሲል ተመጣጣኝ እርምጃ ከመውሰድ ተቆጥቦ በሌላ አቅጣጫ ወደ ፊት በመገስገስ ላይ ይገኛል።
የደሴ ከተማ ነዋሪ ህዝብ የጠላት ምሽግ ላለ መሆን ንብረትህ እና ደህንነትህ እንድትጠብቅ መያዣ እንዲያደርጉህ የፈለጉትን ፋሽስቶች እምቢ እንድትላቸው የትግራይ ሰራዊት ወታደራዊ ኮማንድ በድጋሚ ያሳስባል።
የትግራይ ሰራዊት ወታደራዊ ኮማንድ
ጥቅምት 19 ቀን 2014 ዓ.ም

You must be logged in to post a comment.